በአማራ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን የዘር ማጥፋት አስመልከቶ ለሴናተር ሮይ ዋይደን ገለጻ ተደረገ

የአማራ ማህበር በኦሪገን የስራ አመራርና የቦርድ አባላትን እንዲሁም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የሚወክሉ 12 አባላትን ያካተተ ልዑክ  በአማራ ህዝብና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ በብልጽግናው መንግሰት እየደረሰ ያለውን የዘር ማጥፋት ድርጊት ለህዝብ እንደራሴው ሮይ ዋይደን ገለጻ አደረጉ። የተሰጠው መግለጫ በአማራ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን የጅምላ ጭፍጨፋ፣ ግድያ፣ መፈናቀል፣ ከስራ መሰናበት፣ እገታ፣ ስደት፣ የጋዜጠኞች፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችና ፖለቲከኞች ያለ ፍርድ መታሰርን ያካተተ ነው። የመሰብሰብ፣ ሃሳብን በነጻነት የማራመድና የመያዝ መብት በአገዛዙ ስለመገደቡና ይህን ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብት በሀገሪቱ ህግ መሰረት ለማካሄድ በሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች ላይ አማራ በመሆናቸው ብቻ የዚህ መብት ተሳታፊ እንዳይሆኑ አገዛዙ የሚያደርገውን አምባገነናዊ ድርጊት በማስረጃ በማስደገፍ ማብራሪያ ተሰጥቷል። አረመኔው የብልጽግና መንግስት የአማራ ነው ያለውን ባህል፣ እምነትና ታሪክ እንዴት እያጠፋ እንደሆነ በምስል ማስረጃ ተደግፎ ቀርቧል። የባህል መገለጫዎቹ፣ ቤተ እምነቶቹና ታሪካዊ ቅርሶቹ መውደማቸውን፣ በተለይ የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ከ100 ዓመታት በላይ እድሜ ያላቸውን አብያተ ክርስቲያናት ከእምነቱ ተከታዮቻቸው ጋር መቃጠላቸው ተገልጿል። ከመጋቢት 2015 ዓም በክልሉ አገዛዙ ጦርነት ካወጀ ጊዜ ጀምሮ ከአራት ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች...Read More

የአውሮጳ የሕግና የፍትህ ማዕከል (European Centre for law and Justice ) ባለሥልጣናት ዛሬ ከቀትር በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተፈጸሙ ያሉ ጥቃቶችን የተመለከተ ገለጻ ተደረገ።

የአውሮጳ የሕግና የፍትህ ማዕከል (European Centre for law and Justice ) ባለሥልጣናት ዛሬ ከቀትር በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተፈጸሙ ያሉ ጥቃቶችን የተመለከተ ገለጻ ተደረገ። የአውሮጳ የሕግና የፍትህ ማዕከል ከቀናት በፊት ሽትራስቡርግ ፈረንሳይ በሚገኘው የሕብረቱ ምክር ቤት በጎን በሚካሄድ መድረክ ኢትዮጵያውን ላይ እየተፈጸመ ስላለ ወከባና ጥቃት እንደሚያደምጥ ዐሳውቆ ነበር። በቀጠሮው መሠረትም በዛሬው ዕለት የመድረኩ ዋነኛ ተናጋሪ ልዑል ዶክተር አስፋወሰን አሥራተ፤ በተለይ «በዝምታ የሚፈጸመው የአማራ ስቃይ» በሚል ርዕስ ዝርዝር ገለጻ አድርገዋል። ልዑል ዶክተር አስፋወን አስራተን በማስተዋወቅ የጀመሩት መድረኩን ከጋበዙት የአውሮጳ ምክር ቤት አባላት አንዱ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር፦ «ኢትዮጵያ ውስጥ በአንድ አቅጣጫ ብቻ የእርስ በእርስ ጦርነት ብቻ ያለ ይመስለኝ ነበር» ያሉ ሲሆን፤ ከሚደርሷቸው መረጃዎች ግን ጥቃት ግጭቱ በየቦታው መሰራጨቱን መረዳታቸውን ተናግረዋል። ዶክተር አስፋወሰን በበኩላቸው በገለጻቸው ኢትዮጵያ ውስጥ በሲቪሎች ላይ እየተፈጸመ ነው ያሉትን ጥቃት እና ግድያ መንግሥት ማስቆም አልቻለም ሲሉ ወቅሰዋል። «ብዙ ጊዜ የመንግሥት ሚና ምንድነው እያልኩ እጠይቃለሁ» ያሉት ልጅ ዶክተር አስፋወሰን አስራተ፤ ቅድሚያ የሕዝቡን ደኅንነት ማስከበር የመንግሥት ኃላፊነት እንደሆነ አጽንኦት ሰጥተዋል። የአፍሪቃ ኅብረትን ጨምሮ...Read More

አማራን ለምን?

በአማራ ሕዝብ ላይ የሚፈጸመው ግፍ፣ መፈናቀል እና ጭፍጨፋ በዋነኛነት ከስርዓታዊ የፖሊሲ ልዩነቶች፣ ከመንግስት ኃይሎችና ታጣቂዎች መካከል ከሚካሄደው ከባድ የትጥቅ ግጭት፣ እንዲሁም ብሔር ተኮር ኢላማ ከሚያደርጉ ጥቃቶችና የተጠያቂነት መጥፋት የሚመነጩ ውስብስብ የሰብአዊ መብት ቀውሶች ናቸው። እንደ ዓለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅቶች (የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽንንም ይጨምራል) ሪፖርቶች፣ በጥቃቶቹ እና በግፉ መከሰት ላይ አስተዋጽኦ ከሚያደርጉ በርካታ ምክንያቶች መካከል ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው፡- የኦነግ፣ የሻቢያና የትግራይ ነጻ አውጪ ድርጅቶች የፈጠሩት አሉታዊ ትርክት ኦነግ (የኦሮሞ ነፃነት ግንባር) እ.ኤ.አ በ 1973 በኦሮሞ ብሔርተኞች የተመሰረተ የፖለቲካ ድርጅት ነው ሲሆን ዓላማውም የኦሮሞ ሕዝብ ራሱን በራሱ በነፃነት የማስተዳደር መብት እንዲያረጋግጥ እና ከጭቆና ነፃ ለማውጣት በሚል ዓላማ ነው። ህወሓት (የሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ) በበኩሉ የካቲት 11 ቀን 1967 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ. የካቲት 18 ቀን 1975) በትግራይ ክልል ዴደቢት በረሃ የትጥቅ ትግሉን በመጀመር  የተመሠረተና ዓላማውም በወቅቱ የነበረውን የደርግ ወታደራዊ መንግሥት ጭቆና በመቃወም እና የትግራይን ህዝብ ራስን በራስ የማስተዳደር መብት ለማረጋገጥ የሚል ነበር። ከላይ ለተገለጹት እንደ እንጀራ አባት...Read More

በኦሮምያ አርሲ ዞን የደረሰውን ጭፍጨፋ አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

ከኦሪገን አማራ ማህበር የተሰጠ መግለጫ በኦሮምያ አርሲ ዞን በንጹሃን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምዕመናን ላይ የተፈጸመው የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ ከስርዓቱ ገዳይነት ባህሪይው የመነጨ በመሆኑ ሁሉም የሰው ልጆች ሊያወግዙትና ሊታገሉት የሚገባ ጉዳይ ነው። ይህ የዘር ማጥፋት እንቅስቃሴ እንደ በፊቶቹ ጭፍጨፋዎች ሁሉ በራሱ በአገዛዙ የተዘጋጁና የተፈጸሙ መሆናቸውን በቀላሉ መረዳት ይቻላል። ለዚህም ዋነኛ ማስረጃው ያለምንም ማጣራት የአገዛዙ አፈቀላጤ ሃይሉ አዱኛ ወጥቶ “ኦነግ ሸኔ ፈጸመው” ማለቱና በቀጣይ ቀን ደግሞ “ድርጊቱን የሚያጣራ ልዑክ እልካለሁ” ማለቱ፤ እንዲሁም የአገዛዙ የፕሮፖጋንዳ ሚዲያዎች ከድርጊቱ በፊት ሰብስቦ ምርጫውን ለማደናቀፍ በሃይማኖት ተቋማትና በተከታዮቻቸው ላይ ጥቃት ሊፈጸም ስለሚችል ጉዳዩን እንዳትዘግቡ የሚል አቅጣጫ መስጠቱ ድርጊቱ በዕቅድ ስለመፈጸሙ ማረጋገጫዎች ናቸው። ይህ አረመኔ ገዳይ መንግስት ከመጣ ጊዜ አንስቶ ስንት የአማራ ልጆች ታረዱ፣ ከእነነፍሳቸው በቤታቸው ተቆልፎባቸው ተቃጠሉ፣ ስንቶች በህይዎት ወደ ጥልቅ ጉድጓድ ተጣሉ፣ ስንቶች ቀባሪ አጥተው ለጅብና ለአሞራ ተዳረጉ፣ ስንት አብያተ ክርስቲያናት ተቃጠሉ፣ ስንት ንብረት ወደመ ተዘረፈ፣ ስንት ህዝብ ያለማውን ቀየ ትቶ በአማራነቱ ተሳደደ? ለዚህ ማን ምን አደረገ? መልሱ ምንም ከማይፈይድ መግለጫ በቀር ምንም ነው። እረኛ ተብለው...Read More

ከዓለም ዓቀፍ የአማራ ዲያስፖራ ጥምረት ለአውሮፓ ህብረት የተጻፈ ግልጽ ደብዳቤ

OPEN LETTER FROM A COALITION OF GLOBAL AMHARA DISPORA ORGANIZATIONS June 1, 2026 Ginbot 24, 2018 E.C. Urgent need for reassessment of budgetary assistance for the criminal regime in Ethiopia, currently led by Prime Minister Abiy Ahmed We the undersigned Amhara civic organizations write this open letter to express grave concern over the recent announcement by the European Union (EU) of resumption of budgetary support and strengthened partnership with the Oromo Prosperity Party (OPP) led Prosperity Party (PP) regime of Ethiopia. The announcement mentioned resumption of budget support, economic support, and investments with assurances of future commitments. We understand that the EU has provided extensive humanitarian and development support to the Ethiopian people in the past. However, we strongly believe that unfettered support of any kind to the regime in Ethiopia would be to the detriment of both the Ethiopian people and to the member states of the EU. Below,...Read More