በምስራቅ አርሲ አማራንና የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነትን ትኩረት አድርገው በተፈፀሙ የማንነት ጥቃቶች ከ450 በላይ ንጹሓን ዜጎች መገደላቸውን ኢሰመጉ አስታወቀ

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) በምስራቅ አርሲ አማራንና የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነትን ትኩረት አድርገው በተፈፀሙ የማንነት ጥቃቶች ከ450 በላይ ንጹሓን ዜጎች መገደላቸውን ባወጣው ሪፖርት አስታወቀ። ኢሰመጉ በኦሮሚያ ክልል በምስራቅ አርሲ ዞን በሚገኙ ዘጠኝ ወረዳዎች በተለይ በአማራና በኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታዮችና ተቋማት ላይ በተፈፀሙ ጥቃቶች ቢያንስ 450 ንፁሃን ዜጎች መገደላቸውን ምክር ቤቱ ባወጣው አዲስ ሪፖርት አስታውቋል። ከመስከረም 2021 እስከ ሰኔ 2026 ባለው የምርመራ ጊዜ ውስጥ በተካተተው 158ኛው ልዩ መግለጫ ላይ፣ 37 ገጽ ያለው ሪፖርት አካላዊ ጉዳቶችን፣ የጅምላ እስራቶችን፣ አስገድዶ መድፈርንና በታጠቁ ቡድኖች የተፈፀሙ ሰፊ የንብረት ውድመትን ጨምሮ ሰፊ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን በማስረጃ አስደግፎ በዝርዝር አቅርቧል። ኢሰመጉ በምርመራው የአካል የመስክ ምልከታዎችንና የመረጃ አሰባሰብ መንገዶችን መጠቀሙን ገልጿል። በተጎዱት ዘጠኝ ወረዳዎች የተመዘገበው የሟቾች ቁጥርም እንደሚከተለው ነው፡- መርቲ፡ 117 ሰዎች ሼርካ፡ 116 ሰዎች ጄጁ፡ 101 ሰዎች ካባ፡ 47 ሰዎች ጉና፡ 26 ሰዎች ሆንኮሎ ዋቤ፡ 20 ሰዎች ሙኒሳ፡ 19 ሰዎች አሰኮ፡ 5 ሲቪሎችና 4 የአካባቢው ሚሊሻዎች የአርሲ አለቃ፡ 3 ሰዎች መሆናቸውን ኢሰመጉ የሟቾችን ስምና ማንነት በሪፖርቱ ውስጥ አካቷል።...Read More

በአማራ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን የዘር ማጥፋት አስመልከቶ በአማራ ማህበር ኦሪገን የኦሪገን ሁለተኛ እንደራሴ ለሆኑት ሴናተር ጀፍ መርክሌይ ገለጻ አደረገ።

የአማራ ማህበር ኦረገን በጁን 18 ቀን 2026 ዓ.ም ከሴናተር ሮን ዋይደን ጋር ገለፃ መደረጉ ይታወቃል። በአማራ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን ግፍ ለአሜሪካ የህዝብ እንደራሴዎች የማሳወቅ እንቅስቃሴውን አጠናክሮ በመቀጠል ጁን 30,2026 በኦሪገን የህዝብ እንደራሴ ለሆኑት ጀፍ መርክሌይ እየደረሰ ያለውን የአማራ ህዝብ የዘር ማጥፋት ድርጊት በመረጃ በማስደገፍ ገለጻ ተደርጓል። የአማራ ማህበር በኦሪገን የስራ አመራርና የቦርድ አባላትን እንዲሁም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የሚወክሉ 12 አባላት በአማራ ህዝብና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ በብልጽግናው መንግሰት እየደረሰ ያለውን የዘር ማጥፋት ድርጊት ለማሳወቅ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ አጠናክረው በመቀጠል ጁን 30 ቀን 2026 ዓ.ም ለህዝብ እንደራሴው ጀፍ መርክሌይ ገለጻ አደርገዋል። የተሰጠው መግለጫ በአማራ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን የጅምላ ጭፍጨፋ፣ ግድያ፣ መፈናቀል፣ ከስራ መሰናበት፣ እገታ፣ ስደት፣ የጋዜጠኞች፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችና ፖለቲከኞች ያለ ፍርድ መታሰርን ያካተተ ነው። የመሰብሰብ፣ ሃሳብን በነጻነት የማራመድና የመያዝ መብት በአገዛዙ ስለመገደቡና ይህን ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብት በሀገሪቱ ህግ መሰረት ለማካሄድ በሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችና የህዝብ እንደራሴዎች ላይ አማራ በመሆናቸው ብቻ የዚህ መብት ተሳታፊ እንዳይሆኑ አገዛዙ የሚያደርገውን አምባገነናዊ...Read More