በአማራ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን የዘር ማጥፋት አስመልከቶ በአማራ ማህበር ኦሪገን የኦሪገን ሁለተኛ እንደራሴ ለሆኑት ሴናተር ጀፍ መርክሌይ ገለጻ አደረገ።

የአማራ ማህበር ኦረገን በጁን 18 ቀን 2026 ዓ.ም ከሴናተር ሮን ዋይደን ጋር ገለፃ መደረጉ ይታወቃል። በአማራ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን ግፍ ለአሜሪካ የህዝብ እንደራሴዎች የማሳወቅ እንቅስቃሴውን አጠናክሮ በመቀጠል ጁን 30,2026 በኦሪገን የህዝብ እንደራሴ ለሆኑት ጀፍ መርክሌይ እየደረሰ ያለውን የአማራ ህዝብ የዘር ማጥፋት ድርጊት በመረጃ በማስደገፍ ገለጻ ተደርጓል። የአማራ ማህበር በኦሪገን የስራ አመራርና የቦርድ አባላትን እንዲሁም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የሚወክሉ 12 አባላት በአማራ ህዝብና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ በብልጽግናው መንግሰት እየደረሰ ያለውን የዘር ማጥፋት ድርጊት ለማሳወቅ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ አጠናክረው በመቀጠል ጁን 30 ቀን 2026 ዓ.ም ለህዝብ እንደራሴው ጀፍ መርክሌይ ገለጻ አደርገዋል። የተሰጠው መግለጫ በአማራ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን የጅምላ ጭፍጨፋ፣ ግድያ፣ መፈናቀል፣ ከስራ መሰናበት፣ እገታ፣ ስደት፣ የጋዜጠኞች፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችና ፖለቲከኞች ያለ ፍርድ መታሰርን ያካተተ ነው። የመሰብሰብ፣ ሃሳብን በነጻነት የማራመድና የመያዝ መብት በአገዛዙ ስለመገደቡና ይህን ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብት በሀገሪቱ ህግ መሰረት ለማካሄድ በሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችና የህዝብ እንደራሴዎች ላይ አማራ በመሆናቸው ብቻ የዚህ መብት ተሳታፊ እንዳይሆኑ አገዛዙ የሚያደርገውን አምባገነናዊ...Read More