Blog

በአማራ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለውን የዘር ማጥፋት አስመልከቶ ለሴናተር ሮይ ዋይደን ገለጻ ተደረገ

የአማራ ማህበር በኦሪገን የስራ አመራርና የቦርድ አባላትን እንዲሁም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የሚወክሉ 12 አባላትን ያካተተ ልዑክ  በአማራ ህዝብና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ በብልጽግናው መንግሰት እየደረሰ ያለውን የዘር ማጥፋት ድርጊት ለህዝብ እንደራሴው ሮይ ዋይደን ገለጻ አደረጉ። የተሰጠው መግለጫ በአማራ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን የጅምላ ጭፍጨፋ፣ ግድያ፣ መፈናቀል፣ ከስራ መሰናበት፣ እገታ፣ ስደት፣ የጋዜጠኞች፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችና ፖለቲከኞች ያለ ፍርድ መታሰርን ያካተተ ነው። የመሰብሰብ፣ ሃሳብን በነጻነት የማራመድና የመያዝ መብት በአገዛዙ ስለመገደቡና ይህን ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብት በሀገሪቱ ህግ መሰረት ለማካሄድ በሚንቀሳቀሱ ግለሰቦች ላይ አማራ በመሆናቸው ብቻ የዚህ መብት ተሳታፊ እንዳይሆኑ አገዛዙ የሚያደርገውን አምባገነናዊ ድርጊት በማስረጃ በማስደገፍ ማብራሪያ ተሰጥቷል። አረመኔው የብልጽግና መንግስት የአማራ ነው ያለውን ባህል፣ እምነትና ታሪክ እንዴት እያጠፋ እንደሆነ በምስል ማስረጃ ተደግፎ ቀርቧል። የባህል መገለጫዎቹ፣ ቤተ እምነቶቹና ታሪካዊ ቅርሶቹ መውደማቸውን፣ በተለይ የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ከ100 ዓመታት በላይ እድሜ ያላቸውን አብያተ ክርስቲያናት ከእምነቱ ተከታዮቻቸው ጋር መቃጠላቸው ተገልጿል። ከመጋቢት 2015 ዓም በክልሉ አገዛዙ ጦርነት ካወጀ ጊዜ ጀምሮ ከአራት ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች...Read More

የአውሮጳ የሕግና የፍትህ ማዕከል (European Centre for law and Justice ) ባለሥልጣናት ዛሬ ከቀትር በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተፈጸሙ ያሉ ጥቃቶችን የተመለከተ ገለጻ ተደረገ።

የአውሮጳ የሕግና የፍትህ ማዕከል (European Centre for law and Justice ) ባለሥልጣናት ዛሬ ከቀትር በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ እየተፈጸሙ ያሉ ጥቃቶችን የተመለከተ ገለጻ ተደረገ። የአውሮጳ የሕግና የፍትህ ማዕከል ከቀናት በፊት ሽትራስቡርግ ፈረንሳይ በሚገኘው የሕብረቱ ምክር ቤት በጎን በሚካሄድ መድረክ ኢትዮጵያውን ላይ እየተፈጸመ ስላለ ወከባና ጥቃት እንደሚያደምጥ ዐሳውቆ ነበር። በቀጠሮው መሠረትም በዛሬው ዕለት የመድረኩ ዋነኛ ተናጋሪ ልዑል ዶክተር አስፋወሰን አሥራተ፤ በተለይ «በዝምታ የሚፈጸመው የአማራ ስቃይ» በሚል ርዕስ ዝርዝር ገለጻ አድርገዋል። ልዑል ዶክተር አስፋወን አስራተን በማስተዋወቅ የጀመሩት መድረኩን ከጋበዙት የአውሮጳ ምክር ቤት አባላት አንዱ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር፦ «ኢትዮጵያ ውስጥ በአንድ አቅጣጫ ብቻ የእርስ በእርስ ጦርነት ብቻ ያለ ይመስለኝ ነበር» ያሉ ሲሆን፤ ከሚደርሷቸው መረጃዎች ግን ጥቃት ግጭቱ በየቦታው መሰራጨቱን መረዳታቸውን ተናግረዋል። ዶክተር አስፋወሰን በበኩላቸው በገለጻቸው ኢትዮጵያ ውስጥ በሲቪሎች ላይ እየተፈጸመ ነው ያሉትን ጥቃት እና ግድያ መንግሥት ማስቆም አልቻለም ሲሉ ወቅሰዋል። «ብዙ ጊዜ የመንግሥት ሚና ምንድነው እያልኩ እጠይቃለሁ» ያሉት ልጅ ዶክተር አስፋወሰን አስራተ፤ ቅድሚያ የሕዝቡን ደኅንነት ማስከበር የመንግሥት ኃላፊነት እንደሆነ አጽንኦት ሰጥተዋል። የአፍሪቃ ኅብረትን ጨምሮ...Read More

አማራን ለምን?

በአማራ ሕዝብ ላይ የሚፈጸመው ግፍ፣ መፈናቀል እና ጭፍጨፋ በዋነኛነት ከስርዓታዊ የፖሊሲ ልዩነቶች፣ ከመንግስት ኃይሎችና ታጣቂዎች መካከል ከሚካሄደው ከባድ የትጥቅ ግጭት፣ እንዲሁም ብሔር ተኮር ኢላማ ከሚያደርጉ ጥቃቶችና የተጠያቂነት መጥፋት የሚመነጩ ውስብስብ የሰብአዊ መብት ቀውሶች ናቸው። እንደ ዓለም አቀፍ እና ሀገር አቀፍ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅቶች (የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽንንም ይጨምራል) ሪፖርቶች፣ በጥቃቶቹ እና በግፉ መከሰት ላይ አስተዋጽኦ ከሚያደርጉ በርካታ ምክንያቶች መካከል ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው፡- የኦነግ፣ የሻቢያና የትግራይ ነጻ አውጪ ድርጅቶች የፈጠሩት አሉታዊ ትርክት ኦነግ (የኦሮሞ ነፃነት ግንባር) እ.ኤ.አ በ 1973 በኦሮሞ ብሔርተኞች የተመሰረተ የፖለቲካ ድርጅት ነው ሲሆን ዓላማውም የኦሮሞ ሕዝብ ራሱን በራሱ በነፃነት የማስተዳደር መብት እንዲያረጋግጥ እና ከጭቆና ነፃ ለማውጣት በሚል ዓላማ ነው። ህወሓት (የሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ) በበኩሉ የካቲት 11 ቀን 1967 ዓ.ም. (እ.ኤ.አ. የካቲት 18 ቀን 1975) በትግራይ ክልል ዴደቢት በረሃ የትጥቅ ትግሉን በመጀመር  የተመሠረተና ዓላማውም በወቅቱ የነበረውን የደርግ ወታደራዊ መንግሥት ጭቆና በመቃወም እና የትግራይን ህዝብ ራስን በራስ የማስተዳደር መብት ለማረጋገጥ የሚል ነበር። ከላይ ለተገለጹት እንደ እንጀራ አባት...Read More

በኦሮምያ አርሲ ዞን የደረሰውን ጭፍጨፋ አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

ከኦሪገን አማራ ማህበር የተሰጠ መግለጫ በኦሮምያ አርሲ ዞን በንጹሃን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምዕመናን ላይ የተፈጸመው የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ ከስርዓቱ ገዳይነት ባህሪይው የመነጨ በመሆኑ ሁሉም የሰው ልጆች ሊያወግዙትና ሊታገሉት የሚገባ ጉዳይ ነው። ይህ የዘር ማጥፋት እንቅስቃሴ እንደ በፊቶቹ ጭፍጨፋዎች ሁሉ በራሱ በአገዛዙ የተዘጋጁና የተፈጸሙ መሆናቸውን በቀላሉ መረዳት ይቻላል። ለዚህም ዋነኛ ማስረጃው ያለምንም ማጣራት የአገዛዙ አፈቀላጤ ሃይሉ አዱኛ ወጥቶ “ኦነግ ሸኔ ፈጸመው” ማለቱና በቀጣይ ቀን ደግሞ “ድርጊቱን የሚያጣራ ልዑክ እልካለሁ” ማለቱ፤ እንዲሁም የአገዛዙ የፕሮፖጋንዳ ሚዲያዎች ከድርጊቱ በፊት ሰብስቦ ምርጫውን ለማደናቀፍ በሃይማኖት ተቋማትና በተከታዮቻቸው ላይ ጥቃት ሊፈጸም ስለሚችል ጉዳዩን እንዳትዘግቡ የሚል አቅጣጫ መስጠቱ ድርጊቱ በዕቅድ ስለመፈጸሙ ማረጋገጫዎች ናቸው። ይህ አረመኔ ገዳይ መንግስት ከመጣ ጊዜ አንስቶ ስንት የአማራ ልጆች ታረዱ፣ ከእነነፍሳቸው በቤታቸው ተቆልፎባቸው ተቃጠሉ፣ ስንቶች በህይዎት ወደ ጥልቅ ጉድጓድ ተጣሉ፣ ስንቶች ቀባሪ አጥተው ለጅብና ለአሞራ ተዳረጉ፣ ስንት አብያተ ክርስቲያናት ተቃጠሉ፣ ስንት ንብረት ወደመ ተዘረፈ፣ ስንት ህዝብ ያለማውን ቀየ ትቶ በአማራነቱ ተሳደደ? ለዚህ ማን ምን አደረገ? መልሱ ምንም ከማይፈይድ መግለጫ በቀር ምንም ነው። እረኛ ተብለው...Read More

ከዓለም ዓቀፍ የአማራ ዲያስፖራ ጥምረት ለአውሮፓ ህብረት የተጻፈ ግልጽ ደብዳቤ

OPEN LETTER FROM A COALITION OF GLOBAL AMHARA DISPORA ORGANIZATIONS June 1, 2026 Ginbot 24, 2018 E.C. Urgent need for reassessment of budgetary assistance for the criminal regime in Ethiopia, currently led by Prime Minister Abiy Ahmed We the undersigned Amhara civic organizations write this open letter to express grave concern over the recent announcement by the European Union (EU) of resumption of budgetary support and strengthened partnership with the Oromo Prosperity Party (OPP) led Prosperity Party (PP) regime of Ethiopia. The announcement mentioned resumption of budget support, economic support, and investments with assurances of future commitments. We understand that the EU has provided extensive humanitarian and development support to the Ethiopian people in the past. However, we strongly believe that unfettered support of any kind to the regime in Ethiopia would be to the detriment of both the Ethiopian people and to the member states of the EU. Below,...Read More

አገዛዙ በአማራ ክልል የሚያደርገው እስራትና ግድያ እንደቀጠለ ነው።

የአማራ ማህበር በአሜሪካ በሚያደርገው ጥናት መሰረት ከግንቦት 4 እስከ 10 ቀን 2026 ባለው ሳምንት በአማራ ፋኖ ራስን የመከላከል ሃይል (ፋኖ) እና በኦሮሞ ብልጽግና ፓርቲ አገዛዝ የጋራ ሃይሎች (የገዥ ሃይሎች) መካከል በኢትዮጵያ የተለያዩ አካባቢዎች ውጊያዎች የቀጠሉ ሲሆን በርካታ ሰብአዊ ጥፋቶች ደርሰዋል። በዚህ ሳምንት በአማራ ክልል በሚገኙ ከ28 በላይ በሚሆኑ ወረዳዎች/ከተማ አስተዳደሮች ውስጥ የተከሰቱ ግጭቶችና የመብት ጥሰቶች ተመዝግበዋል። እነዚህ ዞኖች ሰሜን ወሎ፣ ደቡብ ወሎ፣ ሰሜን ሸዋ፣ ምስራቅ ጎጃም፣ ምዕራብ ጎጃም፣ አዊ፣ ሰሜን ጎጃም፣ ደቡብ ጎንደር እና ምዕራብ ጎንደር ይገኙበታል። በኦሮሚያ ክልል በምስራቅ ወለጋ ዞን የተኩስ ልውውጦችም ተመዝግበዋል። በአማራ ክልል በሚገኙ 4 ዞኖች በሚገኙ 7 ወረዳ/ከተማ አስተዳደሮች የዜጎች ጉዳት ደርሷል። እነዚህም በሰሜን ወሎ፣ በሰሜን ሸዋ፣ በምስራቅ ጎጃም እና በደቡብ ጎንደር ዞኖች የሚገኙ ራያ- ቆቦ፣ ቡግና፣ ኤፍራታና- ግድም፣ እንሳሮ፣ መንዝ-ማማ-ምድር፣ ደብረ-ማርቆስ እና የስማዳ ወረዳዎች ይገኙበታል። በአዲስ አበባ ከተማም እስራትና ነጻ እርምጃ የተወሰደባቸው ዜጎች ተመዝግቧል። ይህም ግጭቶች፣ እስራቶችና ግድያዎች ወደ ዋና ከተማዋ እየዘለቀ መሆኑን አመላካች ነው። በሰሜን ወሎ እና ደቡብ ጎንደር ዞኖች በቡግና፣ ስማዳ እና...Read More

ለሰብአዊነት ቅድሚያ ይሰጣል

ፖርትላንድ፡ሚያዚያ 9 ቀን 2018 ዓ.ም የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን)ወደ አንድነት መምጣቱ ለሰብአዊነት የሚሰጠውን ትኩረት ከፍ አድርጎታል ሲሉ የድርጅቱ አመራሮች ገለጹ። ይህ የተገለጸው  የአማራ ማህበር በኦሪገን በአማራ ክልል ሰብአዊ ቀውስን ለመቀነስ ንቅናቄው ምን እየሰራ እንደሆነ ተጠይቆ ለተሰብሳቢዎቹ አመራሮች ማብራሪያ በሰጡበት ስብሰባ ላይ ነው። ንቅናቄው ዓለም ዓቀፍ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎችን አክብሮ የሚሰራ መሆኑም ተረጋግጧል። በቅድሚያ ማብራሪያ የሰጡት የአፋብን ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አስረስ ማረ ሲሆኑ በማብራሪያቸውም ፋኖ የህብረተሰቡ ጥያቄ የነበረውን የአንድነት ጉዳይ በድል ካጠናቀቀ ጊዜ አንስቶ በተፈጥሮም ሆነ በሰው ሰራሽ አደጋዎች ሰዎች እንዳይጎዱ ቀጥታ ድጋፍ ከማድረግ ባለፈ ችግሩን ለሚመለከታቸው አካላት በማድረስና እርዳታ እንዲደርሳቸው በማድረግ በኩል የተሻለ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ድርጅቱም በተመሰረተ በአጭር ጊዜ በርካታ ውሳኔዎችንና ትላልቅ ወታደራዊ ድሎች አስመዝግቧል። ይሁን እንጂ ድርጅቱ ዲያስፖራውን በማደራጀት እና ተገቢው ድጋፍ እንዲደረግ በማድረግ በኩል ብዙ ይቀራል ብለዋል። አገዛዙ ውጊያ ተዋግቶ ያሸነፈበት፣ የተረጋጋ አስተዳደራዊ መዋቅር ዘርግቶ መስራት እንዳይችል ከመደረጉም በላይ ትጥቅና ሥንቅ ከጠላቶቻችን በሚል መርህ ወታደራዊ ትግሎችን በማከናዎን ሁሉንም በድል በማጠናቀቅ ከፍተኛ የሆነ ትጥቅና...Read More

MISS IT NOT!

🚨 የህልውና እና የክብር ጥሪ፡ ለኦሪገን አማራ ማህበር አባላትና ደጋፊዎች "ታሪክ የሚሰራው በሚሳተፉት እንጂ በታዛቢዎች አይደለም!" በቅድሚያ እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። የክርስቶስ ትንሳኤ ለህዝባችን የተስፋ፣ የድልና የነፃነት ብርሃን እንዲሆንልን ከልብ እንመኛለን። ነገር ግን በዓሉን ስናከብር፣ ወገናችን የሚገኝበትን እጅግ አስቸጋሪና ፈታኝ ወቅት መዘንጋት አይገባንም። አሁን ያለንበት ወቅት የቆረጡ ልጆች እንጂ የዳር ተመልካች የማይሻበት ጊዜ ነው። ማህበራችን ይህንን ታሪካዊ ግዴታ ለመወጣት የእያንዳንዱን አባልና ደጋፊ ንቁ ተሳትፎ የግድ ይላል። ለምን መገኘትዎ ግዴታ ነው? * ሶስት ልዩ ተጋባዥ እንግዶች፦ በወቅታዊው የህዝባችን ሁኔታና በቀጣይ ስራዎቻችን ላይ ጥልቅ ትንታኔና መመሪያ የሚሰጡን ሶስት አንጋፋ እንግዶች በሰዓቱ ተገኝተው ንግግር ያደርጋሉ። * የወደፊት አቅጣጫ፦ የስብሰባው ዋና አላማ የማህበራችንን የቀጣይ ጊዜያት ስትራቴጂያዊ እርምጃዎች ለመወሰንና የጋራ አቋም ለመያዝ ነው። * አንድነታችንን ማሳያ፦ በስብሰባው ላይ በብዛት መገኘታችን ለጠላቶቻችን መለኪያ፣ ለወዳጆቻችን ደግሞ ጥንካሬ ነው። 📅 ቀን፦ ዓርብ፣ ኤፕሪል 17፣ 2026 (Friday, April 17) 🕗 ሰዓት፦ በትክክል ምሽት 8:00 PM (Pacific Time) 🔗 የZoom መግቢያ ሊንክ፦ እዚህ ይጫኑና ይግቡ 📌 Meeting ID:...Read More

በዋግኽምራ ዞን በድርቅ ምክንያት ከ4 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ተሰደዱ

በዋግኽምራ ዞን በድርቅ ምክንያት ከ4 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ተሰደዱ አንዳንዶች ልጆቻቸውን ለልመና እያሰማሩ መሆኑ ተገልጧል ህጻናትን ለልመና የሚያሰማሩ አካላት ላይ መንግስት ጥብቅና ሕጋዊ ርምጃ ለመውሰድ የዞን ግብረ ኃይል ማደራጀቱን ዐሳውቋል በአማራ ክልል በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን፣ ፃግብጂ ወረዳ በሚገኙ አራት ቀበሌዎች በተከሰተ ድርቅ ምክንያት ከ4 ሺህ በላይ ሰዎች ቀዬያቸውን ጥለው ወደ ተለያዩ ከተሞች መሰደዳቸውን የአካባቢው ነዋሪዎችና መምህራን ገለጹ። በርካታ ህጻናት ትምህርታቸውን አቋርጠው ከቤተሰቦቻቸው ጋር ወደ ደሴና ሌሎች ከተሞች በመሰደድ በልመና ተግባር ላይ ተሰማርተው እንደሚገኙም ተገልጧል ። በደሴ ከተማ በልመና ላይ የሚገኙ የሁለተኛ ክፍል ተማሪዎች፦ ስደቱ የተከሰተው በአካባቢያቸው የሚበላ ነገር በመጥፋቱና በድርቁ ምክንያት መሆኑን ተናግረዋል። መምህራን በበኩላቸው ስደቱ በመማር ማስተማር ሂደቱ ላይ ከፍተኛ ጫና መፍጠሩን ገልጸው፣ አንዳንዶች ልመናን እንደ ገቢ ምንጭ በመጠቀም ልጆቻቸውን ለልመና እያሰማሩ መሆኑንም ተናግረዋል ። የዞኑ አደጋ መከላከልና ሥራ አመራር ኮሚሽን በበጋው ወቅት ሰብላቸው ለተጎዳባቸው 27 ሺህ ሰዎች የምግብና የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን ገልጿል። የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ምህረት መላኩ እንደገለጹት፦ በትክክል በችግር ምክንያት የተሰደዱትን ነዋሪዎች ወደ ቀዬያቸው በመመለስ ድጋፍ የማድረግ ሥራ እየተሠራ መሆኑን...Read More