እንቁጣጣሽ! መልካም አዲስ አመት

እንኳን ለ2019 ዓ.ም አዲስ ዓመት አደረሳችሁ! የአማራ ማህበር በኦሪገን ለማህበሩ አባላትና ለመላው ኢትየጵያውያን አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ ይላል። ከአሮጌው ዘመን በመማር ለአዲሱ ዓመት አዲስ ትልም በመንደፍ ስኬት የምናሳካበት ዘመን ይሆናል ብሎ ማህበራችን ያምናል። አዲስ ዓመት አዲስ ታሪክ ለመጻፍ የተሰጠን ንጹሕ ገጽ በመሆኑ ለትውልድ የሚሻገር መልካም ስራ መስራት ተገቢ ነው። ትናንትን መለወጥ ባንችልም እንኳን፤ ነገን ግን በአዲስ ማንነትና በጠንካራ ሥራ ማሸብረቅ ዘመን ተሻጋሪ ማድረግ እንችላለን። ዘመን መለወጡ ሳይሆን ቁም ነገሩ በተለወጠው ዘመን ላይ ሁነን በአንድነት የምንሰራው ሥራ ነው ወሳኙ ነገር። አዲሱ ዓመት በህልውና ትግል ውስጥ ላለው ህዝባችን ፍትህ የሚጎናጸፍበት እንዲሆን ማህበራችን ጠንካራ ምኞቱ ነው። ለዚህም ከጠንካራ አባላቱና ደጋፊዎቹ ጋር በመሆን የሰብአዊ ድጋፉን አጠናክሮ ይቀጥላል። በዚህ አጋጣሚ ማህበረሰባችን በክልሉ ላሉ የድርቅ፣ የመፈናቀልና የጦርነት አደጋዎች ለተጋለጡ ወገኖች ድጋፉን እንዲያደርግ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። መልካም አዲስ አመት!   “የቀደመውን ነገር አታስቡ፤ ያለፈውን እርሱ።እነሆ፤ አዲስ ነገር አደርጋለሁ! እርሱም አሁን ይበቅላል፤ አታስተውሉትምን? በምድረ በዳም መንገድ አዘጋጃለሁ፤ በበረሓም ምንጭ አፈልቃለሁ።” ኢሳ 43፡18      

ዘመን በባተ ቁጥር ስለኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር ይነገራል። ለግንዛቤ ቀጣዩን ጽሑፍ አንብቡት።

የኢትዮጵያ ዘመን አቈጣጠር በዲያቆን ኃይለ ኢየሱስ ቢያ መስከረም  ፮ ቀን ፳፻፲ ዓ.ም የዘመን አቈጣጠር ዓመታትን፣ ወራትን፣ ሳምንታትን፣ ዕለታትን፣ ደቂቃን እና ድቁቅ ሰዓታትን በየሥፍራቸው (በየመጠናቸው) የሚገልጽ፤ የሚተነትን፤ የሚለካ የቤተ ክርስቲያን የቍጥር ትምህርት ነው፡፡ እነዚህ ዅሉ ተመርምረው፣ ተመዝነው፣ ተቈጥረው ሲያበቁ ምድብና ቀመር ተሰጥቷቸው የሚገኙበትን ውሳኔና ድንጋጌ የሚያሳውቅ የዘመን አቈጣጠር – ‹ሐሳበ ዘመን› ይባላል፡፡ ዓመታት፣ ወራት፣ ሳምንታት፣ ዕለታትና ሰዓታት የሚለኩት (የሚሠፈሩት፣ የሚቈጠሩት) በሰባቱ መሥፈሪያና በሰባቱ አዕዋዳት ነው፡፡ ሰባቱ መሥፈርታት የሚባሉትም፡- ሳድሲት፣ ኃምሲት፣ ራብዒት፣ ሣልሲት፣ ካልዒት፣ ኬክሮስ እና ዕለት ሲኾኑ ሰባቱ አዕዋዳት ደግሞ፡- ዐውደ ዕለት፣ ዐውደ ወርኅ፣ ዐውደ ዓመት፣ ዐውደ ፀሐይ፣ ዐውደ አበቅቴ፣ ዐውደ ማኅተም እና ዐውደ ቀመር ናቸው፡፡ ዐውደ ዕለት – ከእሑድ እስከ ቅዳሜ ያሉት ሰባቱ ዕለታት ሲኾኑ፤ አውራኅን (ወራትን) ለማስገኘት በዚህ ሲመላለሱ ይኖራሉ፡፡ ዐውደ ወርኅ – በፀሐይ ፴ ዕለታት፣ በጨረቃ ፳፱ ወይም ፴ ዕለታት ናቸው፤ ዓመታትን ለማስገኘት በዚህ ሲመላለሱ ይኖራሉ፡፡ ዐውደ ዓመት – በፀሐይ ቀን አቈጣጠር ፫፻፷፭ ቀን ከ፲፭ ኬክሮስ፤ በጨረቃ አቈጣጠር ፫፻፶፬ ቀን ከ፳፪ ኬክሮስ ነው፡፡ እነዚህ ሦስቱ በዕለት፤ አራቱ ደግሞ...Read More