Blog

ለሰብአዊነት ቅድሚያ ይሰጣል

ፖርትላንድ፡ሚያዚያ 9 ቀን 2018 ዓ.ም የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን)ወደ አንድነት መምጣቱ ለሰብአዊነት የሚሰጠውን ትኩረት ከፍ አድርጎታል ሲሉ የድርጅቱ አመራሮች ገለጹ። ይህ የተገለጸው  የአማራ ማህበር በኦሪገን በአማራ ክልል ሰብአዊ ቀውስን ለመቀነስ ንቅናቄው ምን እየሰራ እንደሆነ ተጠይቆ ለተሰብሳቢዎቹ አመራሮች ማብራሪያ በሰጡበት ስብሰባ ላይ ነው። ንቅናቄው ዓለም ዓቀፍ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎችን አክብሮ የሚሰራ መሆኑም ተረጋግጧል። በቅድሚያ ማብራሪያ የሰጡት የአፋብን ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አስረስ ማረ ሲሆኑ በማብራሪያቸውም ፋኖ የህብረተሰቡ ጥያቄ የነበረውን የአንድነት ጉዳይ በድል ካጠናቀቀ ጊዜ አንስቶ በተፈጥሮም ሆነ በሰው ሰራሽ አደጋዎች ሰዎች እንዳይጎዱ ቀጥታ ድጋፍ ከማድረግ ባለፈ ችግሩን ለሚመለከታቸው አካላት በማድረስና እርዳታ እንዲደርሳቸው በማድረግ በኩል የተሻለ ሥራ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል። ድርጅቱም በተመሰረተ በአጭር ጊዜ በርካታ ውሳኔዎችንና ትላልቅ ወታደራዊ ድሎች አስመዝግቧል። ይሁን እንጂ ድርጅቱ ዲያስፖራውን በማደራጀት እና ተገቢው ድጋፍ እንዲደረግ በማድረግ በኩል ብዙ ይቀራል ብለዋል። አገዛዙ ውጊያ ተዋግቶ ያሸነፈበት፣ የተረጋጋ አስተዳደራዊ መዋቅር ዘርግቶ መስራት እንዳይችል ከመደረጉም በላይ ትጥቅና ሥንቅ ከጠላቶቻችን በሚል መርህ ወታደራዊ ትግሎችን በማከናዎን ሁሉንም በድል በማጠናቀቅ ከፍተኛ የሆነ ትጥቅና...Read More

MISS IT NOT!

🚨 የህልውና እና የክብር ጥሪ፡ ለኦሪገን አማራ ማህበር አባላትና ደጋፊዎች "ታሪክ የሚሰራው በሚሳተፉት እንጂ በታዛቢዎች አይደለም!" በቅድሚያ እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። የክርስቶስ ትንሳኤ ለህዝባችን የተስፋ፣ የድልና የነፃነት ብርሃን እንዲሆንልን ከልብ እንመኛለን። ነገር ግን በዓሉን ስናከብር፣ ወገናችን የሚገኝበትን እጅግ አስቸጋሪና ፈታኝ ወቅት መዘንጋት አይገባንም። አሁን ያለንበት ወቅት የቆረጡ ልጆች እንጂ የዳር ተመልካች የማይሻበት ጊዜ ነው። ማህበራችን ይህንን ታሪካዊ ግዴታ ለመወጣት የእያንዳንዱን አባልና ደጋፊ ንቁ ተሳትፎ የግድ ይላል። ለምን መገኘትዎ ግዴታ ነው? * ሶስት ልዩ ተጋባዥ እንግዶች፦ በወቅታዊው የህዝባችን ሁኔታና በቀጣይ ስራዎቻችን ላይ ጥልቅ ትንታኔና መመሪያ የሚሰጡን ሶስት አንጋፋ እንግዶች በሰዓቱ ተገኝተው ንግግር ያደርጋሉ። * የወደፊት አቅጣጫ፦ የስብሰባው ዋና አላማ የማህበራችንን የቀጣይ ጊዜያት ስትራቴጂያዊ እርምጃዎች ለመወሰንና የጋራ አቋም ለመያዝ ነው። * አንድነታችንን ማሳያ፦ በስብሰባው ላይ በብዛት መገኘታችን ለጠላቶቻችን መለኪያ፣ ለወዳጆቻችን ደግሞ ጥንካሬ ነው። 📅 ቀን፦ ዓርብ፣ ኤፕሪል 17፣ 2026 (Friday, April 17) 🕗 ሰዓት፦ በትክክል ምሽት 8:00 PM (Pacific Time) 🔗 የZoom መግቢያ ሊንክ፦ እዚህ ይጫኑና ይግቡ 📌 Meeting ID:...Read More

በዋግኽምራ ዞን በድርቅ ምክንያት ከ4 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ተሰደዱ

በዋግኽምራ ዞን በድርቅ ምክንያት ከ4 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ተሰደዱ አንዳንዶች ልጆቻቸውን ለልመና እያሰማሩ መሆኑ ተገልጧል ህጻናትን ለልመና የሚያሰማሩ አካላት ላይ መንግስት ጥብቅና ሕጋዊ ርምጃ ለመውሰድ የዞን ግብረ ኃይል ማደራጀቱን ዐሳውቋል በአማራ ክልል በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን፣ ፃግብጂ ወረዳ በሚገኙ አራት ቀበሌዎች በተከሰተ ድርቅ ምክንያት ከ4 ሺህ በላይ ሰዎች ቀዬያቸውን ጥለው ወደ ተለያዩ ከተሞች መሰደዳቸውን የአካባቢው ነዋሪዎችና መምህራን ገለጹ። በርካታ ህጻናት ትምህርታቸውን አቋርጠው ከቤተሰቦቻቸው ጋር ወደ ደሴና ሌሎች ከተሞች በመሰደድ በልመና ተግባር ላይ ተሰማርተው እንደሚገኙም ተገልጧል ። በደሴ ከተማ በልመና ላይ የሚገኙ የሁለተኛ ክፍል ተማሪዎች፦ ስደቱ የተከሰተው በአካባቢያቸው የሚበላ ነገር በመጥፋቱና በድርቁ ምክንያት መሆኑን ተናግረዋል። መምህራን በበኩላቸው ስደቱ በመማር ማስተማር ሂደቱ ላይ ከፍተኛ ጫና መፍጠሩን ገልጸው፣ አንዳንዶች ልመናን እንደ ገቢ ምንጭ በመጠቀም ልጆቻቸውን ለልመና እያሰማሩ መሆኑንም ተናግረዋል ። የዞኑ አደጋ መከላከልና ሥራ አመራር ኮሚሽን በበጋው ወቅት ሰብላቸው ለተጎዳባቸው 27 ሺህ ሰዎች የምግብና የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉን ገልጿል። የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ምህረት መላኩ እንደገለጹት፦ በትክክል በችግር ምክንያት የተሰደዱትን ነዋሪዎች ወደ ቀዬያቸው በመመለስ ድጋፍ የማድረግ ሥራ እየተሠራ መሆኑን...Read More

Meeting reminder

Date: [video width="1920" height="1080" mp4="http://oregonamhara.org/wp-content/uploads/2026/04/Edited-meeting-promo.mp4"][/video] April 17, 2026 Time: At 8 pm Venue: zoom meeting

የስብሰባ ጥሪ

የስብሰባ ጥሪ በኦሪገን የአማራ ማህበር “ተገናኝተን የምንመክርበት ጊዜው አሁን ነው፤ ስለ አማራ የምንመክርበት ጊዜው አሁን ነው፤ በጋራ በመቆም ልዩነት የምንፈጥርበት ጊዜው አሁን ነው” እያለ የስብሰባ ጥሪውን ያስተላልፋል። ዛሬ ተገናኝተን በአንድነት ስለኣማራ ህዝብ መነጋገርና መደገፍ ካልቻልን መቼም ሊሆን አይችልም። ስለዚህ ዛሬ ከትላንትናው በተሻለ በአንድነት በመሆን አስተዋጽኦ ማድረግ ይጠበቅብናል። ስለሀገራችን በተለይም ደግሞ በአማራ ክልል ስላለው ሁኔታ ግንዛቤ መፍጠር አስፈላጊ ነው። በመሆኑም ማህበራችን ከአገር ቤት ካሉ የፋኖ አመራሮችን በቀጥታ በመጋበዝ በክልሉ ስላለው የሰብአዊ አያያዝ፣ የተፈናቃዮች ሁኔታና መደረግ ስላለበት ሰብአዊ ድጋፍ ማብራሪያ እንዲሰጡ ማህበሩ አነጋግሮ ስምምነት ላይ ተደርሷል። ታዲያ ምን ይጠበቃል። የሚጠበቀው በኦሪገንና ዋሽንግተን ቫንኮበር ኗሪ የሆናችሁ የአማራ ተወላጆችና ደጋፊዎች በስብሰባው ላይ መታደም ብቻ። ከዚህም በተጨማሪ ማህበሩ የማህበሩ የስራ እንቅስቃሴ ይቀርባል። በሚደረገው ገለጻ ላይ ተመስርቶ ቀጣይ አቅጣጫ ይቀመጣል። ኑ እኛም የዚህ ታላቅ ህዝብ ልጆች ነንና በጋራ ሁነን ታላቅ ታሪክ እንስራ! በሚያልፍ ህይወት ላይ ሁነን ህያው ሥራ እንስራ። በኦሪገን የአማራ ማህበር Date: April 17 2026 place: Zoom meeting Time: 8 pm

ዓፄ ፋሲለደስ

ዓፄ ፋሲለደስ ወይም ዓፄ ፋሲል (የዙፋን ስማቸው ዓለም ሰገድ) ከአባታቸው ከአፄ ሱሰኒዮስ እና ከእናታቸው ልዕልት ስልጣነ ሞገስ፣ ህዳር 10፣ 1603 (እ.ኤ.አ) ተወለዱ። የነገሱበትም ዘመን ከ1632 እስከ ጥቅምት 18, 1667 (እ.ኤ.አ) ነበር። ንግስና በስረፀ ክርስቶስ በተመራው አመፅ ምክንያት በ1630 ፋሲለደስ ለንግስና ቢበቃም፣ ዘውዱን ግን እስከ 1632 አልጫነም ነበር። ሲመተ ንግስናው በ1632 እንደተገባደደ የመጀመሪያው ስራው የተዋህዶ ቤ/ክርስቲያንን የቀድሞው ቁመና መመለስና የካቶሊኮችን መሬት በመቀማት ከደንካዝ በማባረር በፍሪሞና እንዲወሰኑ ማድረግ ነበር። ወዲያውም በማከታተል ከግብፅ አገር አዲስ ጳጳስ እንዲላክለት በማድረግ በአባቱ ዘመን እንዲደበዝዝ ተደርጎ የነበረውን የግብፅና ኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት ግንኙነት እንዲጸና አደረገ። በኬኒያ የሚገኘው የሞምባሳ ወደብ በፖርቱጋሎች መደብደቡን ሲሰማ፣ የሮማው ፓፓ ከበስትጀርባው ያለበት ሴራ ነው በማለት በምድሩ የነበሩትን የካቶሊክ ጀስዊቶች በመሰብሰብ አባረራቸው።   ጎንደር ከተማ ፋሲለደስ የጎንደር ከተማን በ1636 የኢትዮጵያም ዋና ከተማ አድርጎ እንደቆረቆራት ይታመናል።[1] ከሱ በፊት በአካባቢው ከተማ እንደነበር ወይም እንዳልነበር በታሪክ የተገኘ ማስርጃ እስካሁን የለም። አከታትሎም የፋሲል ግቢንና 44ቱ ታቦታት ተብለው የሚታወቁትን የጎንደር ከተማ አብያተ ክርስቲያናት መሰረት ጣለ። በአፄ ፋሲል ከተመሰረቱት ታዋቂወቹ 44 አብያተ ክርስቲያናት፣ ታዋቂወቹ አደባባይ እየሱስ፣ አደባባይ ተክለ ሃይማኖት፣ አጣጣሚ ሚካኤል፣ ግምጃቤት ማሪያም፣ ፊት ሚካኤል፣ እና ፊት አቦ ይገኙበታል።[2] ያለመታከትም 7 የድንጋይ ድልድዮችን በማሰራት እስካሁን ድረስ ስሙ ሲጠራ...Read More

ከሀገር ቤት የተላከ ደብዳቤ

ይድረስ ለልጆቼ ከአባታችሁ። እንዴው ለመሆኑ ሰላም አላችሁ? ጤንነታችሁ እንዴት ነው? እኛ ደህና ነን። እድሜ ለእናንተ ደህና ነን። እንዴው ሁኔታው ግን ያስፈራል። ግፉ በዛ። ሞት በሁሉም ቤት እየገባ ነው። የኛ ተራም እስኪደርስ ድረስ እንቆዝማለን። ለመሆኑ አማሪካ ችግር ገጠማት እንዴ? በሰልፍ ተናወጠች ብሎ እኮ የአያ ጥላሁን ልጅ በሰፊው አጫወተኝ። ይገርምሃል ትምህርቱን ከዩኒበርስቲ ተመርቆ ከተመለሰ ጊዜ ጀምሮ ስለ ውጭው እና ስለ ሀገራችን በሞባይሉ ይነግረኛል። እንዲያ እሳት የነበረ ተማሪ ኮሌጅ በጥሶ ከእኔ ከሽማግሌው ጋር ሰፈር ለሰፈር ሲውል እንዴት አንጀት ይበላል መሰለህ። የመንግስት ሹማምንት ይመጡና ውትድርና ልውሰድህ እያሉ ስለሚያስቸግሩት እነሱ መጡ በተባለ ቁጥር ጫካ ውስጥ እየዋለ እያደረ ያመልጣቸዋል። ከሰሞኑ መጥተው ቢያጡት ያን ጠንካራ ገበሬ አባቱን ካላመጣኽው እንደፋሃለን ብለውታል። አስጨናቂ ጊዜ ነው ልጆቼ። የራሳችን ጎረቤቶች ወረዳ ሂደው እየጠቆሙ ስንቱን ወጣት ወደ ውትድርና እንዲጋዝ አደረጉት መሰለህ። የእኔ ነገር ለመሆኑ ምን ይፈጠር ብላችሁ ነው በአማሪካ ላይ ሰልፍ የወጣችሁት። ሰው በሃገሩ ስንት ግፍ እየደረሰበት ተሸክሞ ዝም ብሎ የለም እንዴ! መቼም ያልታደለ አማራ ይውጣ አልተባለም አይደል? መቼም የእኛ ጉደኞች እንደሚያደርጉት...Read More

ኢድ ሙባረክ

ለመላው የእስልምና ዕምነት ተከታዮች እንኳን 1447ኛው ኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ኢድ ሙባረክ/ረመዳን ሙባረክ የአማራ ማህበር በኦሪገን

ማህበሩን ለማጠናከር ውይይት ተካሔደ

በኦሪገንና ዋሽንግተን ቫንኮበር የአማራ ማህበር ሥራ አመራሮች ማህበሩን ለማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሄዱ። (ኦሪገን፣ 3/15/2026) በአማራ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን ሁሉን አቀፍ የሰብአዊ ቀውስ ላይ የአማራ ተወላጆች የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ለማስቻል እየተሰራ ነው።  በኦሪገን ሀገረ ግዛት ውስጥ በርካታ የአማራ ተወላጆችና ደጋፊዎች ይኑሩ እንጂ በአንድነት ተሰባስበው  አስተዋጽኦ ከማድረግ አንጻር ብዙ እንደሚቀር ተወያይተዋል። ይህንን የዝምታ አካሄድ ለመስበርና ለማሰባሰብ የተለያዩ መንገዶችን በመጠቀም አባላቱን ለማሰባሰብ በጥንካሬ ለመስራት ተወያይተዋል። በኦሪገንና ዋሽንግተን ቫንኮበር ግዛት ውስጥ የሚኖሩ አማራዎችንና ደጋፊዎችን በመለየት በአካል፣ በስልክና በሌሎች የሚዲያ አማራጮችን በመጠቀም ማህበሩ እስካሁን ያደረጋቸውን የሰብአዊ ድጋፎችና የመሳሰሉ ስራዎችን በማስረዳት ሁሉም የበኩሉን አስተዋጽኦ ቢያደርግ ደግሞ የበለጠ ሥራ መሥራት እንደሚቻል ግንዛቤ በመፍጠር አባላቱን የማሰባሰብና የማስፋት ስራዎችን አጠናክረው ለመስራት አጽንኦት ሰጥተዋል። ከዚህም በተጨማሪ ሀገር ቤት ያለውን የአማራ ክልል ነባራዊ ሁኔታና የሰብአዊ አያያዝ በተመለከተ በቦታው የሚገኙ የፋኖ አመራሮችን በመጋበዝ ለአባላቱ ማብራርያ እንዲሰጡ ለማድረግ እንዲሰራ ወስነዋል። የአማራ ህዝብ በዘርፈ ብዙ ችግሮች ውስጥ ያለ መሆኑን መረዳት አስፈላጊ መሆኑን የተነጋገሩ ሲሆን በኦሪገን የሚኖሩ ሁሉ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ጥሪ...Read More

War updates from Amhara Region, Ethiopia – February 16th to 22nd, 2026

Overview   For the week of February 16th to 22nd, 2026, fighting between the Amhara Fano self-defense force (Fano) and Oromo Prosperity Party regime joint forces (regime forces) has continued in various parts of Amhara Region in Ethiopia.   This week battle events and rights violations were recorded in more than 36 woreda/city administrations across 10 zonal administrations in Amhara Region. These zones included Wag-Hemra, North Wollo, South Wollo, North Shewa, East Gojjam, West Gojjam, North Gojjam, South Gonder, Central Gonder and West Gonder Zones.   Civilian casualties were recorded in 15 woreda/city administrations across 7 zonal administrations in Amhara Region. These included Gubalafto, Mekdela, Wegdi, Efratana-Gidim, Minjar-Shenkora, Kewet, Antsokiyana-Gemza, Gozamin, Finote-Selam, Jabi-Tehnan, Wemberima, Quarit, North Mecha, Bahir-Dar-Zuriya and Alefa Woredas in North Wollo, South Wollo, North Shewa, East Gojjam, West Gojjam, North Gojjam and Central Gonder Zones.   Arrests were recorded in Kobo City and Raya-Alamata Woredas of North...Read More