ዓፄ ፋሲለደስ

ዓፄ ፋሲለደስ ወይም ዓፄ ፋሲል (የዙፋን ስማቸው ዓለም ሰገድ) ከአባታቸው ከአፄ ሱሰኒዮስ እና ከእናታቸው ልዕልት ስልጣነ ሞገስ፣ ህዳር 10፣ 1603 (እ.ኤ.አ) ተወለዱ። የነገሱበትም ዘመን ከ1632 እስከ ጥቅምት 18, 1667 (እ.ኤ.አ) ነበር። ንግስና በስረፀ ክርስቶስ በተመራው አመፅ ምክንያት በ1630 ፋሲለደስ ለንግስና ቢበቃም፣ ዘውዱን ግን እስከ 1632 አልጫነም ነበር። ሲመተ ንግስናው በ1632 እንደተገባደደ የመጀመሪያው ስራው የተዋህዶ ቤ/ክርስቲያንን የቀድሞው ቁመና መመለስና የካቶሊኮችን መሬት በመቀማት ከደንካዝ በማባረር በፍሪሞና እንዲወሰኑ ማድረግ ነበር። ወዲያውም በማከታተል ከግብፅ አገር አዲስ ጳጳስ እንዲላክለት በማድረግ በአባቱ ዘመን እንዲደበዝዝ ተደርጎ የነበረውን የግብፅና ኢትዮጵያ አብያተ ክርስቲያናት ግንኙነት እንዲጸና አደረገ። በኬኒያ የሚገኘው የሞምባሳ ወደብ በፖርቱጋሎች መደብደቡን ሲሰማ፣ የሮማው ፓፓ ከበስትጀርባው ያለበት ሴራ ነው በማለት በምድሩ የነበሩትን የካቶሊክ ጀስዊቶች በመሰብሰብ አባረራቸው።   ጎንደር ከተማ ፋሲለደስ የጎንደር ከተማን በ1636 የኢትዮጵያም ዋና ከተማ አድርጎ እንደቆረቆራት ይታመናል።[1] ከሱ በፊት በአካባቢው ከተማ እንደነበር ወይም እንዳልነበር በታሪክ የተገኘ ማስርጃ እስካሁን የለም። አከታትሎም የፋሲል ግቢንና 44ቱ ታቦታት ተብለው የሚታወቁትን የጎንደር ከተማ አብያተ ክርስቲያናት መሰረት ጣለ። በአፄ ፋሲል ከተመሰረቱት ታዋቂወቹ 44 አብያተ ክርስቲያናት፣ ታዋቂወቹ አደባባይ እየሱስ፣ አደባባይ ተክለ ሃይማኖት፣ አጣጣሚ ሚካኤል፣ ግምጃቤት ማሪያም፣ ፊት ሚካኤል፣ እና ፊት አቦ ይገኙበታል።[2] ያለመታከትም 7 የድንጋይ ድልድዮችን በማሰራት እስካሁን ድረስ ስሙ ሲጠራ...Read More

ከሀገር ቤት የተላከ ደብዳቤ

ይድረስ ለልጆቼ ከአባታችሁ። እንዴው ለመሆኑ ሰላም አላችሁ? ጤንነታችሁ እንዴት ነው? እኛ ደህና ነን። እድሜ ለእናንተ ደህና ነን። እንዴው ሁኔታው ግን ያስፈራል። ግፉ በዛ። ሞት በሁሉም ቤት እየገባ ነው። የኛ ተራም እስኪደርስ ድረስ እንቆዝማለን። ለመሆኑ አማሪካ ችግር ገጠማት እንዴ? በሰልፍ ተናወጠች ብሎ እኮ የአያ ጥላሁን ልጅ በሰፊው አጫወተኝ። ይገርምሃል ትምህርቱን ከዩኒበርስቲ ተመርቆ ከተመለሰ ጊዜ ጀምሮ ስለ ውጭው እና ስለ ሀገራችን በሞባይሉ ይነግረኛል። እንዲያ እሳት የነበረ ተማሪ ኮሌጅ በጥሶ ከእኔ ከሽማግሌው ጋር ሰፈር ለሰፈር ሲውል እንዴት አንጀት ይበላል መሰለህ። የመንግስት ሹማምንት ይመጡና ውትድርና ልውሰድህ እያሉ ስለሚያስቸግሩት እነሱ መጡ በተባለ ቁጥር ጫካ ውስጥ እየዋለ እያደረ ያመልጣቸዋል። ከሰሞኑ መጥተው ቢያጡት ያን ጠንካራ ገበሬ አባቱን ካላመጣኽው እንደፋሃለን ብለውታል። አስጨናቂ ጊዜ ነው ልጆቼ። የራሳችን ጎረቤቶች ወረዳ ሂደው እየጠቆሙ ስንቱን ወጣት ወደ ውትድርና እንዲጋዝ አደረጉት መሰለህ። የእኔ ነገር ለመሆኑ ምን ይፈጠር ብላችሁ ነው በአማሪካ ላይ ሰልፍ የወጣችሁት። ሰው በሃገሩ ስንት ግፍ እየደረሰበት ተሸክሞ ዝም ብሎ የለም እንዴ! መቼም ያልታደለ አማራ ይውጣ አልተባለም አይደል? መቼም የእኛ ጉደኞች እንደሚያደርጉት...Read More

ኢድ ሙባረክ

ለመላው የእስልምና ዕምነት ተከታዮች እንኳን 1447ኛው ኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ኢድ ሙባረክ/ረመዳን ሙባረክ የአማራ ማህበር በኦሪገን

ማህበሩን ለማጠናከር ውይይት ተካሔደ

በኦሪገንና ዋሽንግተን ቫንኮበር የአማራ ማህበር ሥራ አመራሮች ማህበሩን ለማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሄዱ። (ኦሪገን፣ 3/15/2026) በአማራ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን ሁሉን አቀፍ የሰብአዊ ቀውስ ላይ የአማራ ተወላጆች የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ለማስቻል እየተሰራ ነው።  በኦሪገን ሀገረ ግዛት ውስጥ በርካታ የአማራ ተወላጆችና ደጋፊዎች ይኑሩ እንጂ በአንድነት ተሰባስበው  አስተዋጽኦ ከማድረግ አንጻር ብዙ እንደሚቀር ተወያይተዋል። ይህንን የዝምታ አካሄድ ለመስበርና ለማሰባሰብ የተለያዩ መንገዶችን በመጠቀም አባላቱን ለማሰባሰብ በጥንካሬ ለመስራት ተወያይተዋል። በኦሪገንና ዋሽንግተን ቫንኮበር ግዛት ውስጥ የሚኖሩ አማራዎችንና ደጋፊዎችን በመለየት በአካል፣ በስልክና በሌሎች የሚዲያ አማራጮችን በመጠቀም ማህበሩ እስካሁን ያደረጋቸውን የሰብአዊ ድጋፎችና የመሳሰሉ ስራዎችን በማስረዳት ሁሉም የበኩሉን አስተዋጽኦ ቢያደርግ ደግሞ የበለጠ ሥራ መሥራት እንደሚቻል ግንዛቤ በመፍጠር አባላቱን የማሰባሰብና የማስፋት ስራዎችን አጠናክረው ለመስራት አጽንኦት ሰጥተዋል። ከዚህም በተጨማሪ ሀገር ቤት ያለውን የአማራ ክልል ነባራዊ ሁኔታና የሰብአዊ አያያዝ በተመለከተ በቦታው የሚገኙ የፋኖ አመራሮችን በመጋበዝ ለአባላቱ ማብራርያ እንዲሰጡ ለማድረግ እንዲሰራ ወስነዋል። የአማራ ህዝብ በዘርፈ ብዙ ችግሮች ውስጥ ያለ መሆኑን መረዳት አስፈላጊ መሆኑን የተነጋገሩ ሲሆን በኦሪገን የሚኖሩ ሁሉ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ጥሪ...Read More