Month: February 2026
A reminder, Saturday 14th of February 2026
Amhara Association Of Oregon is inviting you to a scheduled Zoom meeting. Topic: General conference Time: Feb 14, 2026 08:00 PM Pacific Time (US and Canada) Join Zoom Meeting https://us06web.zoom.us/j/81548770702?pwd=xN3RTgrrXufVYRvS9uikvnOl1bZW5X.1 Meeting ID: 815 4877 0702 Passcode: 134457 --- One tap mobile +13462487799,,81548770702#,,,,*134457# US (Houston) +16694449171,,81548770702#,,,,*134457# US Join instructions https://us06web.zoom.us/meetings/81548770702/invitations?signature=EFkS87OTVN2MHEZUlT2y88QcMnlco0hhfKL_VVwK7Hc
እንኳን ለዐቢይ ጾምና ለሮመዳን ጾም አደረሳችሁ
በዚህ ሳምንት የሁለት አበይት አብያተ ዕምነቶች ሁለት ታላላቅ ጾሞች ተከታትለው ይጀመራሉ። ሰኞ የካቲት 9 ቀን 2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማንያን የሚጀምሩት ሊቀ ካህን ኢየሱስ ክርስቶስ ጾሞ አማንያን ይጾሙት ዘንድ የተሰጠው ዐቢይ ጾም ወይም የሆዳዴ ጾም ይጀምራል። ከሁለት ቀን በኋላ ረቡዕ የካቲት 11 ቀን 2018 ዓ.ም ደግሞ የእስልምና እምነት ተከታዮች የሚጾሙት የታላቁ የሮመዳን ጾም ይጀመራል። በኦሪገን የአማራ ማህበር እንኳን ለጾሙ በሰላም አደረሳችሁ ይላል። ነቢዩ ኢሳይያስ (58፤6-7) በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶ ስለጾም እንዲህ ይላል። “እኔስ የመረጥኩት ጾም ይህ አይደለምን? የበደልን እስራት ትፈቱ ዘንድ፣ የቀንበርንስ ጠፍር ትለቅቁ ዘንድ፤ የተገፉትንስ አርነት ትሰድዱ ዘንድ፣ ቀንበሩንስ ሁሉ ትሰብሩ ዘንድ አይደለምን? እንጀራህንስ ለተራበ ትቆርስ ዘንድ፣ ስደተኞችንና ድሆች ወደ ቤትህ ታገባ ዘንድ፣ የተራቆቱትንስ ብታይ ታለብሰው ዘንድ፣ ከሥጋ ዘመድህ እንዳትሸሸግ አይደለምን?” ወንጌለኛው ቅዱስ ማቲዎስም (25፤35) ጾማችን ከጠብና ከሙግት በመራቅ ብቻ ሳይሆን መልካም ነገር በመስራት መሆን እንዳለበት የዓለም ቤዛ ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ስብከቱ ያሰተማረውን እንዲህ ያዘክራል። “ተርቤ፣ አብልታችሁኛልና፣ ተጠምቼ አጠጥታችሁኛል፣ እንግዳ ሁኜ ተቀብላችሁኛልና፣ ታርዤ አልብሳችሁልኛልና፣ ታምሜ ጠይቃችሁኛልና፣ ታስሬ ወደ እኔ...Read More
ሰምተዋል?
ሰምተዋል? በኦሪገን የአማራ ማህበር አጠቃላይ ስብሰባ በመጪው ቅዳሜ በኦን ላይን መጥራቱን? ከቤትዎ ሁነው በእጅ ሞባይልዎ ወይም በሚመችዎ የመገናኛ መሣሪያ በመጠቀም ስብሰባውን ይታደሙ። አደራ እንዳይቀሩ። ማህበርዎን ያጠናክሩ! አንድነት ኃይል ነው!
የአገዛዙ የግፍ ግድያ ባህር ዳር ከተማ!
በአማራ ሕዝብ ላይ የዘር ጭፍጨፋ እየፈፀመ ያለው አገዛዝ ምንም አይነት የፖለቲካ ተሳትፎ የሌላቸውን የሕክምና ዶክተሮችን፣ የነቁ አማራዎችንና ባለሐብቶችን በየቀኑ ከቤታቸው እየተጎተተ እያወጣ ማረዱን ቀጥሏል:: በመሆኑም ትላንት በቀን 26/05/2018ዓ.ም ዶ/ር ፀጋሁን ስሜ የሚባልን በምሥራቅ ጎጃም፣ የደብረወርቅ ተወላጅና የባህር ዳር ከተማ ቀበሌ 14 ነዋሪ እንዲሁም የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ሠራተኛ የነበረውን ጥዋት ሥራ ለመግባት በጉዞ ላይ እያለ በአገዛዙ ወታደሮች ይያዛል። የአገዛዙ ወታደሮች ከያዙት በሗላ ወደ ቤቱ መልሰው በመውሰድ በቤቱ ፍተሻ ያደርጋሉ። ቤቱን በመፈተሽ ምንም ነገር ያላገኙት ወታደሮች ዶ/ር ፀጋሁንን ወደ ቤዛዊት ቤተመንግሥት አካባቢ ወስደው ገድለው ጥለውታል። የአገዛዙ ወታደሮች ዶ/ር ፀጋሁንን በአሰቃቂ ሁኔታ ከገደሉ በሗላ በማን አለብኝነት በራሱ ስልክ ለባለቤቱ በመደወል አስከሬኑን እንድትወስድ ይነግሯታል:: ዶ/ር ፀጋሁንን ምን እንዳነጋገሩት ባይታወቅም ከሳምንት በፊት የአማራ ክልል ጤና ቢሮው ኃላፊ የሆነው አብዱልከሪም መንግሥቱ ለብቻው ቢሮ እንዳነጋገረውና ከቢሮ ሲወጣም ጥሩ ስሜት እንዳልነበረው ጓደኞቹ ይናገራሉ:: ቤቱ ሲፈተሽም ምንም አይነት መረጃ እንዳልተገኘና የአገዛዙ ወታደሮችም የወሰዱት ማስረጃ እንደሌለ የዶ/ር ፀጋሁን ቤተሰቦች አረጋግጠዋል። በክልሉ ዋና ከተማ በባህር ዳር እንዲህ አይነት አሰቃቂ ግድያዎች...Read More
Great Ethiopian Renaissance Dam (GERD)
Barbados' Prime Minister, Mia Mottley testimony on GERD with Trevor Nooah [video width="1920" height="1080" mp4="http://oregonamhara.org/wp-content/uploads/2026/02/GERD.mp4"][/video]
