የአማራን አንድነት ማጠናከር አንገብጋቢ ጉዳይ ነው
አንድነታችን ማጠናከር ወቅቱ የሚጠይቀው አንገብጋቢ ጉዳይ ነው ሲሉ በኦሪገን የአማራ ተወላጆች ገለጹ። በኦሪገን የአማራ ማህበር አጠቃላይ ስብሰባ ላይ አባላቱ እንደገለጹት በአማራ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን የሰብአዊ ቀውስ በሚቻለው መጠን ለመደገፍም ሆነ ለዓለም ድምጽ ለማሰማት በጋራ መቆም ወሳኝ መሆኑ በአጽንኦት አባላቱ ገልጸዋል። በ2025 ዓ.ም ማህበሩ በርካታ ስራዎችን መስራቱን በቀረበው ሪፖርት ለማወቅ ተችሏል። ከተሰሩ ስራዎች መካከልም በአገዛዙ በአማራ ህዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍ ለኦሪገን መንግስትና ለፌዴራል መንግስቱ የህዝብ እንደራሴዎች ተገቢው መረጃ እንዲደርሳቸው ተደርጓል። ከዚህም በተጨማሪ ለተፈናቃይ ወገኖች ድጋፍ የሚውል የገንዘብ ማሰባሰብ ሥራ ተሰርቷል። የአባላት ቁርጠኝነት ተጠናክሮ እንዲቀጥል የማህበሩ አመራር የተለያዩ መንገዶችን በመጠቀም ለማሰባሰብ ተሞክሯል። ይሁን እንጂ ጊዜን ሰጥቶ በቁርጠኝነት የመሰባሰብና የሚጠበቀውን ያህል አስተዋጽኦ ማድረግ አልተቻለም። አባላቱ በበኩላቸው የመረጃ ክፍተቶች እንደነበሩ ጠቁመው ይህን ክፍተት በማረም አጠናክሮ መቀጠል አስፈላጊ መሆኑን ትኩረት ተሰጥቶታል። በመንግስት እየተመራ በአማራ ላይ የሚፈጸመውን ግፍ እየተከታተሉ ለአባላቱ፣ ለተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦችና ድርጅቶች፣ ለአሜሪካ ባለስልጣናት በማሳወቅ፣ የምናገኘውን ሚዲያ በመጠቀም ድምጻችንን በማሰማት ግፉ ፍጻሜ እንዲደርስና የአማራ ህዘብ ህልውና እንዲረጋገጥ በትጋት እንደሚሰራ አጽንኦት ተሰጥቶታል። የአማራ...Read More
